ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን መሳተፍ
በአሜሪካን ሀገር ዋሽግንተን ዲሲ በሚገኘው የአሜሪካ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ዘርፍ ማህበራት ንግድ ምክር ቤት፤በኢትዮ-ፕሮሞሽን ኤል.ኤል.ሲ ከሄሌዝ ኤቨንትስ ጋር በጋራ በመተባበር የተዘጋጀውና እ.ኤ.አ ከሴፕቴምበር 24-25/2022 ለሁለት ቀናት የሚቆየው ዓለም አቀፍ የምግብ፤የመጠጥና የባህል ፌስቲቫል መካሔድ ጀምሯል፡፡
በዚሁ ዝግጅት ላይ በድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የሚመራ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኮከቤ ቁምቢ እንዲሁም የማርኬቲንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግሩም መሥፍንን ያከተተ ቡድን የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ አዲሱን ብላክ ዲር ዊስኪን ጨምሮ ተወዳጅ ምርቶቻችንን እያስተዋወቀ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና ተቀማጭነታቸውን አሜሪካን ሀገር ያደረጉ የተለያዩ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ጥራት መለያችን ነው!!
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
189 total views, 1 views today