ዜና
በአሜሪካን ሀገር ዋሽግንተን ዲሲ በሚገኘው የአሜሪካ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮ-ፕሮሞሽን ኤል.ኤል.ሲ፤ከሄሌዝ ኤቨንትስ እና ከኢትዮጵያ ዘርፍ ማህበራት ንግድ ምክር ቤት ጋር በጋራ በመተባበር የተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የምግብ፤የመጠጥና የባህል ፌስቲቫል መስከረም ከ14-15 ቀን 2015 ዓ.ም መከናወኑ ይታወሳል፡፡
ይህንኑ ዝግጅት የአሜሪካን ድምጽ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል በደረጀ ደስታ አዘጋጅነት በመስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት 3፡00 ሰዓት ዜና በንግድና ምጣኔ ሀብት ክፍለ ጊዜው የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካን ተሳትፎ በማጉላት በሰፊው ዘገባውን አቅርቦታል፡፡ ከአሜሪካን ድምጽ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል የተወሰደውን ዝርዝር ዜና አብሮ በተያያዘው ቪዲዮ እና በቀጣይም ድርጅታችንን የሚመለከተውን ዋና ዝግጅት እንዲመለከቱ እንጋብዛለን፡፡
ጥራት መለያችን ነው!!
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
619 total views, 3 views today