የማህበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር!!!
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በሚያደርገው ጥረት አጠገባችን ለሚገኘው የመካኒሳ አካባቢ አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመማር–ማስተማር ሂደቱን የሚደግፉ አጠቃላይ ግምታቸው ከሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር በላይ የሆኑና ብዛታቸው ሁለት መቶ አርባ የፕላስቲክ ወንበሮች፤ስልሳ የፕላስቲክ ጠረጴዛዎች እንዲሁም በሦሰት ዙር የሚለገስ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ የንፅህና መጠበቂያ ሞዴሶች የድርጅታችን ከፍተኛ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባት አማካኝነት ለት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር ወ/ሮ ብሌን የካቲት 2/2014 ዓ.ም እንዲረከቡ ተደርጓል፡፡
በወቅቱም ድርጅታችን በተለይ የአካባቢያችን ማህበረሰብ በመደገፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚቀጥል በዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የተገለፀ ሲሆን ድጋፉን የተረከቡት የት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር ወ/ሮ ብሌን በት/ቤቱ ማህበረሰብ ሥም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡
ጥራት መለያችን ነው!!
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ
650 total views, 3 views today