National Alcohol & Liquor Factory

ዓለም አቀፍ ዕውቅና!!

ዓለም አቀፍ ዕውቅና!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በአለም 130 ሀገራት በሚገኙ 3500 በላይ ድርጅቶችን በያዘውና ዓለም አቀፍ ዕውቅና በመስጠት በሚታወቀው WORLDCOB 2022 BIZZ AWARD ተሸላሚ መሆኑን መግለፃችን ይታወቃል፡፡

  በዚህም መሰረት ይህንኑ ከፍተኛ ሽልማት WORLDCOB .. ከኖቬምበር 11-12/2022 በአሜሪካ ሂውስተን ቴክሳስ ከተማ ባዘጋጀው ዝግጅት ላይ የድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ እና ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ / ኮከቤ ቁምቢ በመገኘት ተቀብለዋል፡፡ በወቅቱም የድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ 2022 WORLD LEADER BUISNESS PERSON የተሰኘውን የዕውቅና ሰርተፍኬት ተበርክቶላቸዋል፡፡

ጥራት መለያችን ነው!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 292 total views,  2 views today

ዜና – ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን መሳተፍ

ዜና

  በአሜሪካን ሀገር ዋሽግንተን ዲሲ በሚገኘው የአሜሪካ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮ-ፕሮሞሽን ኤል.ኤል.ሲ፤ከሄሌዝ ኤቨንትስ እና ከኢትዮጵያ ዘርፍ ማህበራት ንግድ ምክር ቤት ጋር በጋራ በመተባበር የተዘጋጀው ዓለም አቀፍ የምግብ፤የመጠጥና የባህል ፌስቲቫል መስከረም ከ14-15 ቀን 2015 ዓ.ም መከናወኑ ይታወሳል፡፡

   ይህንኑ ዝግጅት የአሜሪካን ድምጽ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል በደረጀ ደስታ አዘጋጅነት በመስከረም 18 ቀን 2015 ዓ.ም ምሽት 3፡00 ሰዓት ዜና በንግድና ምጣኔ ሀብት ክፍለ ጊዜው የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካን ተሳትፎ በማጉላት በሰፊው ዘገባውን አቅርቦታል፡፡  ከአሜሪካን ድምጽ የአማርኛው ዝግጅት ክፍል የተወሰደውን ዝርዝር ዜና አብሮ በተያያዘው ቪዲዮ እና በቀጣይም ድርጅታችንን የሚመለከተውን ዋና ዝግጅት እንዲመለከቱ እንጋብዛለን፡፡

ጥራት መለያችን ነው!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 376 total views,  3 views today

ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን መሳተፍ

ዓለም አቀፍ ኤግዚቢሽን መሳተፍ

በአሜሪካን ሀገር ዋሽግንተን ዲሲ በሚገኘው የአሜሪካ ካቶሊክ ዩኒቨርሲቲ በኢትዮጵያ ዘርፍ ማህበራት ንግድ ምክር ቤት፤በኢትዮ-ፕሮሞሽን ኤል.ኤል.ሲ ከሄሌዝ ኤቨንትስ ጋር በጋራ በመተባበር የተዘጋጀውና እ.ኤ.አ ከሴፕቴምበር 24-25/2022 ለሁለት ቀናት የሚቆየው ዓለም አቀፍ የምግብ፤የመጠጥና የባህል ፌስቲቫል መካሔድ ጀምሯል፡፡

 በዚሁ ዝግጅት ላይ በድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የሚመራ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኮከቤ ቁምቢ እንዲሁም የማርኬቲንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ግሩም መሥፍንን ያከተተ ቡድን የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ አዲሱን ብላክ ዲር ዊስኪን ጨምሮ ተወዳጅ ምርቶቻችንን እያስተዋወቀ በመሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ በፌስቲቫሉ ላይ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና ተቀማጭነታቸውን አሜሪካን ሀገር ያደረጉ የተለያዩ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ድርጅቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡

ጥራት መለያችን ነው!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 325 total views,  3 views today

አስደሳች ዜና

THE BIZZ AWARDS

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ በሆነውና 15 ዓመታት በላይ የድርጅቶችን አፈጻጸም በተለያየ መለኪያዎች በመመዘን እውቅና በመስጠት በሚታወቀውና 130 ዓለም ሀገራት በመስራት ላይ በሚገኘው እንዲሁም 3500 በላይ ታዋቂ አለም አቀፍ አምራች ድርጅቶች አባል ባሉት WORLD CONFIDERATION OF BUSINESSES, A winner of the most important business excellence award in the world, THE BIZZ AWARDS አሸናፊ መሆኑን ለድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ በድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ጄሱስ ሞራን .. ነሐሴ 29/2022 በፃፈው ደብዳቤ በማሳወቁ የተሰማንን ከፍተኛ ደስታ እየገለጽን ይህም የድርጅታችን ሥራ አመራር ቦርድ፤ሥራ አመራርና የመላው ሠራተኛ ጠንካራ አመራር እና ቅንጅት ውጤት ነው፡፡


ይህ ውጤት የተገኘው ድርጅታችን በሥራ አመራር ጥራት ፤የተቀናጀ የአሰራር ሥርዓቶች ትግበራ፤በምርት ጥራት እንዲሁም በትርፋማነትና ውጤማነት ውስጥ ባሉ ዝርዝር መስፈርቶች መሰረት ያለበት የአፈፃፀም ደረጃ ተለክቶ የተገኘ በመሆኑ አሁንም በድጋሚ እንኳን ደስ አለን እያልን በቀጣይም ድርጅታችንን ከዚህ የበለጠ አፈጻጸም ደረጃ ላይ እንደምናደርሰው ያለንን ሙሉ እምነት እንገልፃለን፡፡

ጥራት መለያችን ነው!!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 362 total views,  3 views today

ማህበራዊ ኃሊፊነትን የመወጣት ተግባር!!

ማህበራዊ ኃሊፊነትን የመወጣት ተግባር!!

ብሔራዊ አሌኮሌና አረቄ ፋብሪካ በሰበታ ከተማ ቀበላ 07 ከስድስት ነጥብ ስድስት ሚሉዮን ብር በሊይ ወጪ በማድረግ አካባቢው ማህረሰብ ያስገነባቸውን አሥራ አምስት ሼዶች አጠናቅቆ የሰበታ ከተማ ከንቲባ ክብርት / ዓሌፊያ አብድርሃማን፤ክቡር አቶ ቶልሳ በኦሮሚያ ብሔራዊ ክሌሊዊ መንግሥት የገንዘብና ኢኮኖሚ ሌማት ቢሮ ኃሊፊ እና የብሔራዊ አሌኮሌና አረቄ ፋብሪካ የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ፤ክቡር አቶ ሐብታሙ ሃይ ሚካዔሌ የመንግስት ሌማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዲ ዋና ዲይሬክተር፤ጥሪ የተረገሊቸው የመንግስት ሥራ ኃሊፊዎች፤የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ እና ሥራ አመራር አባሊት እንዱሁም የአካባቢው ማህበረሰብ ተወካዮች በተገኙበት ሚያዚያ 4 ቀን 2014 . አስመርቆ የሼዶቹን ቁሌፍ ሰበታ ከተማ ከንቲባ ክብርት / ዓሌፊያ አብድርሃማን አስረክቧሌ፡፡

 

 የድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የብሔራዊ አሌኮሌና አረቄ ፋብሪካ በአሌኮሌ መጠጡ ኢንደስትሪ የሚገኝ አንጋፋ የመንግሥት ሌማት ድርጅት መሆኑን ገሌፀው ድርጅታችን በአገር አቀፍ ረጃ ገበታ ሀገር፤ሸገር ማስዋብ፤ታሊቁ ህዲሴ ግድባችን ሀገር መከሊከያ ሠራዊት፤ተፈናቃ ወገኖቻችን፤ መካኒሳ አካባቢ ነዋሪዎች የተረጉ እና በማዕድ ማጋራት አማካኝነት ረጋቸውን በርካታ ድጋፎች በምሳላነት በመጠቀስ የሼድ ግንባታ ሥራውን አጠናቅቆ ድርጅታችን በማስረከቡ የተሰማቸውን ስታ በመገሌጽ ሥራው በወቅቱና በጥራት እንዱጠናቀቅ ተሳተፉት አካሊት በሙለ ምስጋናቸውን አቅርበዋሌ፡፡ ጥራት ያችን ነው!! ብሔራዊ አሌኮሌና አረቄ ፋብሪካ!!

 519 total views,  2 views today

ማህበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር!!

ማህበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር!!

   ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ ከበቅሎ ቤት ሰፈር ተወላጆችና ከዳግም ትንሳዔ ወንድማማቾች ማህበር ጋር በመሆን በአዲስ መልክ የተገነባውን የ፶ አለቃ ቸርነት መንገሻ እና የወ/ሮ ሸዋዬ መኖሪያ ቤት የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚን ጨምሮ ከፍተኛ የሥራ አመራር አባላት ፤የወረዳው አመራር ተወካዮች፤የብስራት ኤፍ.ኤም ራዲዮ ባለቤት አቶ መሰለ መንግስቱ፤የማህበሩ ተወካዮችና የአካባቢው ነዋሪዎች በተገኙበት አስመርቆ ለወ/ሮ ሸዋዬ አስረክቧል፡፡

 በወቅቱም የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በአልኮል መጠጡ ኢንዱስትሪ የሚገኝ የመንግሥት ልማት ድርጅት መሆኑንና ያለውን አንጋፋነትና ብቁ ተወዳዳሪነት በአጭሩ ለታዳሚዎች አብራርተዋል፡፡ በተጨማሪም ድርጅታችን በአገር አቀፍ ደረጃ ለገበታ ለሀገር፤ለሸገር ማስዋብ፤ለታላቁ ህዳሴ ግድባችን ፤ለሀገር መከላከያ ሠራዊት እና በማዕድ ማጋራት አማካኝነት ያደረጋቸውን በርካታ ድጋፎች ለአብነት ከመጠቀሳቸውም በላይ ለመካኒሳ አካባቢ ነዋሪዎች የተደረጉ የኮሚኒቲ ፖሊሲንግ ጽ/ቤት እና የኮብል ስቶን መንገድ ግንባታዎችን በተጨማሪ በምሳሌነት በመግለጽ ይህ ሥራም የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባር ዋነኛ አካል መሆኑን በመጥቀስ ወ/ሮ ሸዋዬን እንኳን ደስ አለዎት በማለት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የድርጅታችን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ በበኩላቸው ሥራው የፈጠራባቸውን ደስታ በመግለጽ ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ መሰል የማህበራዊ ኃላፊነት ተግባራትን ማከናወኑን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመጥቀስ የቤቱን ካርታ ለወ/ሮ ሸዋዬ በማስረከብ የእንኳን ደስ አለዎት በማለት መልዕክታቸውን በተጨማሪ አስተላልፈዋል፡፡

በዚህም ወቅት ለመኖሪያ ቤቱ ግንባታ ጉልህ አስተዋጽኦ ያደረጉ ድርጅቶችና የማህበሩ አባላት የዕውቅና ሰርተፍኬት የተበረከተላቸው ሲሆን የድርጅታችን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ እና ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኮከቤ ቁምቢ እንዲሁም አቶ ተረፈ ሶርሱ ይገኙበታል፡፡

ጥራት መለያችን ነው!!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 487 total views,  3 views today

የማህበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር!!!

የማህበራዊ ኃላፊነትን የመወጣት ተግባር!!!

 

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ የማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በሚያደርገው ጥረት አጠገባችን ለሚገኘው የመካኒሳ አካባቢ አንደኛ ደረጃ /ቤት የመማርማስተማር ሂደቱን የሚደግፉ አጠቃላይ ግምታቸው ከሁለት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር በላይ የሆኑና ብዛታቸው ሁለት መቶ አርባ የፕላስቲክ ወንበሮች፤ስልሳ የፕላስቲክ ጠረጴዛዎች እንዲሁም በሦሰት ዙር የሚለገስ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ ሰላሳ የንፅህና መጠበቂያ ሞዴሶች የድርጅታችን ከፍተኛ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባት አማካኝነት ለት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር / ብሌን የካቲት 2/2014 . እንዲረከቡ ተደርጓል፡፡

 

በወቅቱም ድርጅታችን በተለይ የአካባቢያችን ማህበረሰብ በመደገፍ ማህበራዊ ኃላፊነቱን መወጣት እንደሚቀጥል በዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የተገለፀ ሲሆን ድጋፉን የተረከቡት የት/ቤቱ ምክትል ርዕሰ መምህር / ብሌን በት/ቤቱ ማህበረሰብ ሥም ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

 

ጥራት መለያችን ነው!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 650 total views,  3 views today

ዓለም አቀፍ ቀኖችን ማክበር!!!

ዓለም አቀፍ ቀኖችን ማክበር!!!

የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት በማስተላለፍ የዕለቱን መርሃ-ግብር በይፋ ካስጀመሩ በኃላ በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚከበሩትን የዓለም ኤድስ ቀን ( መሪ ቃል፡-አገልግሎታችንን ለተጠቃሚዎች በእኩልነት በማድረስ ወረርሽኙን እንግታ!!) ፤18ኛው ዓለም አቀፍ የሙስና መከላከል ቀን ( መሪ ቃል፡- በሥነ-ምግባር የታነፀ አመራር ከሙስና ለፀዳች ኢትዮጵያ!! ) ፤ ዓለም አቀፍ የነጭ ሪቫን ቀን ( ሠላም ይስፈን በሴቶችና ህጻናት ላይ የሚደርስ ጥቃት ይቁም!! ) በድርጅታችን መሰብሰቢያ አዳራሽ ጥር 16/2014 ዓ.ም ሠራተኞች አክብረዋል፡፡ በዚህም ወቅት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ፕሮግራሞች የተከናወኑ ሲሆን በምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ወ/ሮ ኮከቤ ቁምቢ- ሥነ-ምግባርን በተመለከተ፤በሥርዓት ፆታ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ እመቤት ስማችው ሥርዓተ-ፆታንና ፆታዊ ጥቃትን በተመለከተ እንዲሁም የኤች.አይ.ቪ ኤድስ በሽታ ባህሪያትና መከላከያ መንገዶችን በተመለከተ በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ጤና ቢሮ ከፍተኛ ጤና ባለሙያ በአቶ ስንታየሁ ግንዛቤ ማስጨበጫ እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም የድርጅታችን የ2014 ዓ.ም መጀመሪያ ስድስት ወራት አጠቃላይ የኦፕሬሽን ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ተከናውኗል፡

 572 total views,  1 views today

ዜና

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ እንኳን ደህና መጣችሁ እያለ ከፍተኛ ጥራት ባላቸው ምርቶቹ እንድትዝናኑ በአክብሮት ይጋብዛል!!!
ጥራት መለያችን ነው!!
ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 814 total views,  3 views today

የብሔራዊ ብላክ ዲር ዊስኪ ማስተዋወቅ

አዲሱ ብሔራዊ ብላክ ዲር ዊስኪ ምርታችን ታዋቂ ደንበኞቻችን እና ወኪሎቻችን በተገኙበት በደርጅታች ዋና መስሪያ ቤት ነሐሴ 20/2013 . ከተዘጋጀ ፕሮግራም በኋላ በይፋ ወደ ገበያ መግባቱና በጥራቱም ተወዳጅነትን እያገኘ መጥቷል፡፡

   ቅዳሜ መስከረም 29/2014 . ከጧቱ 430 ጀምሮ በኢትዮጵያ ቱሪስ ንግድ ሥራ ድርጅት ዋና መሥሪያ ቤት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች እና ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የብሔራዊ ብላክ ዲር ዊስኪ የማስተዋወቅ ሥራ በተሳካ ሁኔታ የተናወነ ሲሆን በወቅቱም የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር እንግዶች ጥራቱንና ደረጃውን በተመለከተ ለሰጣችሁን አዎንታዊ አስተያየት ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡

ጥራት መለያችን ነው!!

ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ

 749 total views,  3 views today

Contact Us

Mexico Square Behind Addis Ababa Technical College & Mekanissa
info@nalf.com.et, national.alcohol@gmail.com
+251 115 516 999 / +251 115 516 190
+251 115 513 299

Our Location