National Alcohol & Liquor Factory

Year 2012 E.C

Year 2012 E.C

የብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በልደታ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 10 አካባቢ ለሚገኙ 46 አባወራዎች በሁለት መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ ብር ያሰራውን ዘመናዊ መፀዳጃና መታጠቢያ ቤት አጠናቅቆ ለነዋሪዎቹ አስረከበ፡፡

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ መሥፍን አባተ በርክክብ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በሀገራችን አልኮል መጠጥ አምራች ኢንዱስትሪ ውስጥ አንጋፋ፤ዘመናዊና ከፍተኛ የማምረት አቅም ያለው የመንግሥት ልማት ድርጅት መሆኑን ጠቅሰው የአልኮል መጠጥ ምርት ዋና ግብዓት የሆነውን ንፁህ አልኮልን ጨምሮ የተለያዩ አልኮል መጠጦችን እና እሳት አልኮል በከፍተኛ ጥራት በተፈለገው መጠን አምርቶ ለደንበኞቹ በማቅረብ  የሚታወቅ አትራፊ የመንግሥት ልማት ድርጅት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም በአሁኑ ወቅት በሀገራችን የተከሰተውን የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመከላከል የእሳት አልኮል ምርትን ለገበያ ከማቅረብ ባሻገር  የእጅ ንፅህና መጠበቂያ ሳኒታይዘር በአዲስ መልክ አምርቶ ለገበያ ማዋሉን ገልፀዋል፡፡ ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ በፕሮጀክት አፈፃፀም ብቃት እንዳለው እና ይህም ዛሬ ተጠናቅቆ ለርክክብ የበቃው  ሥራ አንዱ ማስረጃ መሆኑን በምረቃው ወቅት አብራርተዋል፡፡ የማህረሰቡን ችግር የሚፈቱ ተመሳሳይ ሥራዎች በቀጣይነት እንደሚሰሩ ቃል ገብተው የተሰራውን መታጠቢያና መፀዳጃ ቤት በእንክብካቤ መያዝ ላይ ህብረተሰቡ ልዩ ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡

ድርጅታችን የማህበራዊ ኃላፊነቱን በተገቢው ሁኔታ እየተወጣ ያለ ድርጀት ሲሆን ለዚሁ ዓላማ ከፍተኛ በጀት በየዓመቱ በመመደብ የተለያዩ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ላልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ እያደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፋብሪካው የመኖሪያ አካባቢያቸው ምቹ ያልሆነና ለችግር የተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎችን ድጋፍ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አብራርተዋል፡፡

በዚህም መሰረት በልደታ ክፍለ ከተማ በወረዳ 10 አካባቢ የሚኖሩ 46 አባወራዎች ከረጅም ዓመታት በፊት በበጎ አድራጎት ድርጅት የተሰራላቸው መፀዳጃ ቤት ከአገልግሎት ውጪ በመሆኑ ድጋፍ እንዲደርግላቸው በጠየቁት መሰረት የድርጅቱ ሥራ አመራር ተመልክቶ ለፕሮጅክቱ ከ236 ሺህ ብር በላይ ወጪ በማድረግ እና በዘመናዊ መልክ ሰርቶ በማጠናቀቅ ሚያዝያ 20 ቀን 2012 ዓ.ም የወረዳ 10 አስተዳደር ኃላፊዎች በተገኙበት አስመርቆ ለአካባቢው ነዋሪዎች አስረክቧል፡፡

የልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ተፈሪ መርዲሳ በበኩላቸው የተጠቀሱትን አባወራዎች ችግር ድርጅቱ ተመልክቶና ካለው ውሱን በጀት ቀንሶ በመመደብ ይህንን ጥራቱን የተበቀ መታጠቢያና መፀዳጃ ቤት ገንብቶ በማስረከቡ የተሰማቸውን ከፍተኛ ደስታ በወረዳው አስተዳዳር ስም ገልፀዋል፡፡ በተጨማሪም መሰል የመንግስት ልማት ድርጅቶችንና ባለሀብቶችን በማስተባበር የማህረሰቡን ችግር ፈቺ  የሆኑ ተመሳሳይ ሥራዎች በቀጣይ መሰራት እንዳለባቸውና ወረዳውም ለዚህ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡

የወረዳ 10 አካባቢ ነዋሪ የሆኑት እና የመፀዳጃ ቤቱ ሥራ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል የሆኑት አቶ ተክለሚካዔል ታደሰ በበኩላቸው ከረጅም ዓመታት በፊት ተሰርቶ በአሳዛኝ ሁኔታ አገልግሎት መስጠት ያልቻለውን መፀዳጃ ቤት በአዲስ መልክ ለማሰራት ድጋፍ ለማግኘት ያልሄዱበት ድርጅትና ያላንኳኩት ቢሮዎች እንዳልነበሩ ገልፀው ብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ ግን በአጭር ጊዜ ይህንን የመሰለ ጥራቱን የጠበቀ መታጠቢያና መፀዳጃ ቤት ሰርቶ በማስረከቡ የተሰማቸውን ደስታ የሚገልፁበት ቃል እንደሚያጥራቸውና ይህም ከድርጅቱ ሠራተኞች ጀምሮ እሰከ ከፍተኛ ኃላፊዎች ያላቸውን ትጋትና ቀናነት እንደሚያሳይ ከዚህም ሌሎች ድርጅቶች ሊማሩበት እንደሚገባ ያላቸውን ሃሳብ ገልፀዋል፡፡

በብሔራዊ አልኮልና አረቄ ፋብሪካ ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት ረገድ በርካታ ተግባራት ተከናውኗል፣

  • ልደታ ክ/ከተማ የወረዳ 8 ሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ጽ/ቤት ወላጅ ለሌላቸው ህጻናት የደብተር መግዢያ የሚሆን 10,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • በልደታ ክፍለ ከተማ 5፣ በላፍቶ ክ/ከተማ 5 እና በሰበታ 5 በጠቅላላው ለ15 ወላጆቻቸውን በኤች.አይ ቪ/ኤድስ ላጡ ህፃናት በየወሩ ለእያንዳንዳቸው የ600 ብር በድምሩ የ84,000 ብር (ለ10 ህፃናት ድጋፍ ማድረግ የተጀመረው ከህዳር ወር ጀምሮ ነው፡፡) እንዲሁም ለበዓል መዋያ እና የትምህርት ቁሳቁስ መግዣ ብር 40,000 በአጠቃላይ ብር 124,000 ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለሰበታ ከተማ ልዩ ፍላጎት ትምህርት መምህራን ኮሌጅ 10,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፤
  • በመንግስት የልማት ድርጅቶች ይዞታና አስተዳደር ኤጀንሲ የዕድሜ ባለጸጎችን ለመደገፍ በተደረገው ጥሪ መሰረት 50,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለአቢሲኒያ አካል ጉዳተኞች ሴቶችና ህፃናት ልማት ድርጅት ለትምህርት ቁሳቁስ መግዣነት የሚውል ብር 15,000 ስፖንሰር ተደርጓል፡፡
  • የኦሮሚያ ልማት ማህበር ፊንፊኔ ቅርንጫፍ በተለያዩ ቦታዎች ለሚረዳቸው አቅም ለሌላቸው ተማሪዎች ድጋፍ እንዲደረግ ባቀረበው ጥያቄ መሰረት በገንዘብ 10,000ብር ድጋፍ እንዲደረግ ተደርጓል፡፡
  • ለኦሮሚያ ወጣቶች ማህበር፡ – 10,000 ብር ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡
  • ለአማራ ልማት ማህበር 50,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለሰበታ ከተማ አስተዳደር 30,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለጋሞ ልማት ማህበር 20,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለመቆዶኒያ የአረጋውያን እና የአዕምሮ ህመምተኛ ማዕከል ህንጻ ግንባታ የሚውል  100,000 ብር እና የመግቢያ   ትኬት መግዢያ  30,000 ብር በጠቅላላው 130,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡ በተጨማሪም ሁሉም የድርጅቱ ቋሚ ሰራተኞች ከደመወዛቸው በየወሩ ተቆራጭ ተደርጎ ለማዕከሉ ድጋፍ የተደረገ ሲሆን በአጠቃላይ በዓመቱ ብር 157,950 ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለኢትዮጵያ ደረጃዎች ኤጀንሲ 25,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • በድርጅታችን ሙሉ ድጋፍ በ237,000 ብር ወጪ በልደታ ክፍለ ከተማ በወረዳ 10 አካባቢ አርባ አምስት አባወራዎች የተገነባውን ዘመናዊ የገላ መታጠቢያና መፀዳጃ ቤት የክፍለ ከተማው አስተዳደር ተወካዮች በተገኙበት በማስመረቅ ለማህረሰቡ የማስረከብ ሥራ ተከናውኗል፡፡
  • ትኩረት ለሴቶች ማህበር 30,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • በልደታ ክፍለ ከተማ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ማዕከል 30,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለዳሞት የህፃናት ማሳደጊያ 10,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት የኦሮሚያ አርብቶ አደር እና አካባቢ ልማት ኮሚሽን 30,000 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • የድርጅቱ ፋብሪካዎች በሚገኙባቸው በልደታ ክፍለ ከተማ፣በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማና በሰበታ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ በሀገራችን በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለችግር የተጋለጡና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በማዘጋጀት 340 ለሚሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ለእያንዳንዳቸው 25ኪሎ ግራም የጤፍ ዱቄት፣25ኪሎ ግራም የስንዴ ዱቄት እና አምስት ሊትር ዘይት በጠቅላላ የዋጋ ግምቱ 702,931.20 ብር የሚያወጣ ድጋፍ ተደርጓል፡፡

በድርጅታችን የኮሮና ቫይረስ /covid-19/ ለመከላከል በሚደረገው ሀገር አቀፍ ርብርብ ለመደገፍ የእሳት አልኮል (Denature Alcohol) እና ሳኒታይዘር በነፃ ድጋፍ የተደረገላቸው የመንግስት ተቋማትና የበጎ አድራጎት ድርጅቶች

  • (የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት)በኮሮና ቫይረስ ለተጠረጠሩና ተጠቂ ለሆኑ ግለሰቦች ማቆያ ሆስፒታሎች፡- 700 ሊትር እሳት አልኮል
  • የታላቁ ህዳሴ ግድብ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት፡- 500 ሊትር እሳት አልኮል
  • የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ (13 ወረዳዎች)፡- 200 ሊትር እሳት አልኮል
  • የልደታ ክፍለ ከተማ (10 ወረዳዎች)፡- 200 ሊትር እሳት አልኮል
  • መቄዶኒያ የአረጋውያንና የአዕምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል፡- 600 ሊትር እሳት አልኮል
  • ሙዳይ የበጎ አድራጎት ድርጅት፡- 100 ሊትር እሳት አልኮል
  • ሜሪጆይ፡- 300 ሊትር እሳት አልኮል
  • መሠረት የበጎ አድራጎት ድርጅት፡- 100 ሊትር እሳት አልኮል
  • ጠብታ አምቡላንስ፡- 200 ሊትር እሳት አልኮል
  • ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለሰበሰባቸው የጎዳና ተዳዳሪዎች፡- 400 ሊትር እሳት አልኮል እና 10,000 ብር የሚያወጣ 2100 ሳሙና ድጋፍ ተደርጓል፡፡
  • ለዮአብ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. ( የታክሲ ህዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርቶችን በአልኮል ለማጽዳት)፡- 500 ሊትር እሳት አልኮል
  • ለከሰም ስኳር ፋብሪካ፡- 500 ሊትር እሳት አልኮል
  • በኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ህጻናት መርጃ፡- 200 ሊትር እሳት አልኮል
  • የልደታ ክፍለ ከተማ (ከተለያዩ ሀገራት ለሚመጡ ግለሰቦች ለተዘጋጀው የ14 ቀን ማቆያ ቦታዎች በህዳሴ፣ ተስፋ እና ባልቻ አባነፍሶ ት/ቤት፡- 200 ሊትር እሳት አልኮል
  • ለኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ፡- 200 ሊትር እሳት አልኮል
  • የኢትዮጵያ የኩላሊት ህመምተኞች እጥበት በጎ አድራጎት ድርጅት፡- 300 ሊትር እሳት አልኮል
  • ለሰበታ ከተማ የጤና አጠባበቅ ጽ/ቤት፡- 100 ሊትር እሳት አልኮል
  • በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ለኤካ ኮተቤ ሆስፒታል (በኮሮና ቫይረስ ለተጠረጠሩና ተጠቂ ለሆኑ ግለሰቦች ማቆያ ሆስፒታል)፡- 400 ሊትር እሳት አልኮል
  • በልደታ ክፍለ ከተማ ለወረዳ 8 አስተዳደር ስር ለሚገኙ በኮሮና ቫይረስ ለተጠረጠሩና ለተጠቂ ለሆኑ ግለሰቦች ማቆያ ሆስፒታሎች፡- 100 ሊትር እሳት አልኮል
  • የድርጅቱ ፋብሪካዎች በሚገኙባቸው በልደታ ክፍለ ከተማ፣በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማና በሰበታ ከተማ አስተዳደር በወቅቱ በሀገራችን በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ምክንያት ለችግር የተጋለጡና በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም በማዘጋጀት 340 ለሚሆኑ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ለሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ለእያንዳንዳቸው አንድ ሳኒታይዘር እና አንድ ሊትር እሳት አልኮል ድጋፍ ተደርጓል፡፡

በአጠቃላይ ከላይ ያልተጠቀሱትን ጨምሮ በዓይነት የተደረገው ድጋፍ ሲታይ የእሳት አልኮል/denature alcohol/=9,115 ሊትር ሲሆን ወደ ብር ሲቀየር 444,925 ብር ፤ 2,992 ባለ 250ሲሲ ሳኒታይዘር ወደ ብር ሲቀየር 194,480 ብር ድጋፍ ተደርጓል፡፡

  • ለንፋስ ስ/ክ/ከተማ 5000 ችግኝ በብር 190,750 ብር ተገዝቶ ድጋፍ ተደርጓል::

በበጀት ዓመቱ በአጠቃላይ በብርና በአይነት ድጋፍ የተደረገው ጠቅላላ ብር 2,635,368 ድጋፍ ተደርጓል፡፡

 2,184 total views,  2 views today

Contact Us

Mexico Square Behind Addis Ababa Technical College & Mekanissa
info@nalf.com.et, national.alcohol@gmail.com
+251 115 516 999 / +251 115 516 190
+251 115 513 299

Our Location